Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ሀገር አቀፍ የምርምር ኮንፍረንስ በጂንካ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 4፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ”የጥናትና የምርምር ስራዎች ለዕውቀት ሽግግርና ለዘላቂ ልማት” በሚል ርዕስ የተዘጋጀው አራተኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ኮንፍረንስ በጂንካ ዩኒቨርሲቲ እየተካሄደ ይገኛል።

በኮንፈረንሱ በኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ልማቶች ላይ ያተኮሩ የተለያዩ ጥናታዊ ጽሁፎች እንደሚቀርቡ ተገልጿል።

ለሁለት ቀናት በሚቆየው የምርምር ኮንፍረንሱ የጂንካ ዩኒቨርሲቲ የቦርድ ሰብሳቢና የባህልና ስፖርት ሚኒስትር አቶ ቀጀላ መርዳሳ፣ የቦርዱ አባላት ፣የደቡብ ክልልና ደቡብ ኦሞ ዞን ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ፣ የዩኒቨርሲቲው አመራሮችና ምሁራን እየተሳተፉ ነው።

ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የተወጣጡ ጥናት አቅራቢዎችና ሌሎች ባለድርሻ አካላት እንደተገኙም ኢዜአ ዘግቧል።

Exit mobile version