Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፐሪሚየር ሊግ መሪው ቅዱስ ጊዮርጊስ ነጥብ ጣለ

አዲስ አበባ፣ግንቦት 4፣2014 (ኤፍ ቢሲ) በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ዛሬ በተካሄደ ጨዋታ መሪው ቅዱስ ጊዮርጊስ ነጥብ ጥሏል፡፡

ፈረሰኞቹ ረፋድ 4 ሰዓት በባህርዳር ስታዲየም ከወላይታ ዲቻ ጋር ባደረጉት ጨዋታ ያለምንም ግብ አቻ ተለያይተዋል፡፡

ቅዱስ ጊዮርጊስ ነጥብ መጣሉን ተከትሎ የነጥብ ልዩነቱን ለማጥበብ እና ወደ ዋንጫ ፉክክር ለመመለስ የፋሲል ከነማ አሸናፊነት ተጠባቂ ነው፡፡

 

Exit mobile version