Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አቶ ሙስጠፌ የኮንትሮባንድ ንግድን መከላከል በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ከጸጥታ አካላት ጋር ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 6፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሃመድ ከፌደራልና ከክልል ፀጥታ ሃይሎች አመራሮች ጋር ተወያይተዋል፡፡

በውይይታቸውም በሶማሌ ክልል የሚስተዋለውን የኮንትሮባንድ ንግድ መከላከል በሚቻልበት ጉዳይ ላይ መክረዋል፡፡

ከዚህ ባለፈም የክልሉን አጠቃላይ ሰላም እና ደህንነት ይበልጥ ማጠናከር በሚያስችሉ ጉዳዮች ዙሪያ መምከራቸውን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

Exit mobile version