Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ሉሲዎቹ ነገ ከዛንዚባር አቻቸው ጋር ጨዋታቸውን ያደርጋሉ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 24፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ሴቶች ብሔራዊ ቡድን ነገ 7 ሰዓት ከዛንዚባር አቻው ጋር ጨዋታውን ያደርጋል ፡፡

በሴካፋ ውድድር ላይ ለመሳተፍ ስፍራው የደረሰው ብሔራዊ ቡድኑ ዛሬ ረፋድ ላይ የመጀመሪያ ልምምዱን አከናውኗል።

በምድብ ሁለት ከታንዛኒያ፣ ዛንዚባር እና ደቡብ ሱዳን ጋር የተደለደለው ቡድኑ የመጀመሪያ ጨዋታውን ነገ 7 ሰዓት ከዛንዚባር አቻው ጋር እንደሚደርግ ሶከር ኢትዮጵያ ዘግቧል።

Exit mobile version