Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የአፍሪካ ኅብረት እና የአውሮፓ ምክር ቤት አባላት በዩክሬን ጉዳይ ላይ ተወያዩ

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 24፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፍሪካ ኅብረት እና የአውሮፓ ኅብረት ምክር ቤት አባላት በዩክሬን ጉዳይ ላይ በበይነ-መረብ ተወያይተዋል፡፡

የወቅቱ የአፍሪካ ኅብረት ሊቀ-መንበር የሴኔጋሉ ፕሬዚዳንት ማኪ ሳል ÷ ስብሰባቸው በዩክሬን በተከሰተው ግጭት ምክንያት ባጋጠመው የምግብ አቅርቦት ችግር ላይ መሆኑን አመላክተዋል፡፡

ማኪ ሳል ስብሰባውን ያካሄዱት ዩክሬንና ሩሲያን በጥቂት ሣምንታት ውስጥ ለመጎብኘት ፍላጎት እንዳላቸው ለሀገራቱ ከገለጹ ከቀናት በኋላ መሆኑ ተመላክቷል፡፡

የጉብኝታቸው ትኩረትም ሃገራቱ ወደ አፍሪካ ይልኩት የነበረውን የጥራጥሬ ምርት እንዲቀጥሉ ለማግባባት ያለመ መሆኑን ሲ ጂ ቲ ኤን ዘግቧል፡፡

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version