Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ሁለተኛው የኦሮሚያ ክልል የአቃቤ ህጎች አጠቃላይ ጉባኤ እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ግንቦት 28፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ሁለተኛው የኦሮሚያ ክልል የአቃቤ ህጎች አጠቃላይ ጉባኤ በጅማ ከተማ እየተካሄደ ነው፡፡

የኦሮሚያ ጠቅላይ አቃቤ ህግ አዱኛ አህመድ የክልሉ አቃቤ ህግ ቢሮ ስለ ህግና የፍትህ ስርአት ግንዛቤ ለመፍጠር፣ የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ፣ የወንጀል ህግን ተፈፃሚ ለማድረግና የህዝብና የመንግስትን ጥቅም ለማስጠበቅ እንደተቋቋመ ተናግረዋል።

በመሆኑም እየተደረገ ያለው ጉባኤ የአቅቤ ህጎችን አቅም በማጎልበት ተልዕኳቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ያደርጋልም ነው ያሉት።

በጉባኤው ላይ የፌደራል እና የክልል ከፍተኛ አመራሮች የተገኙ ሲሆን “ሃገራዊ ምክክርና የሌሎች ሃገራት ተሞክሮ ” የሚል ፅሁፍ ቀርቦ ምክክር እየተደረገበት ይገኛል።

በሙክታር ጠኃ

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version