አዲስ አበባ፣ ሰኔ 12፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በፓሪስ ዳይመንድ ሊግ በ5 ሺህ ሜትር ውድድር ሰለሞን ባረጋ አሸንፏል፡፡
በወንዶች ምድብ በተካሄደው 5 ሺህ ሜትር የፓሪስ ዳይመንድ ሊግ ውድድር ሰለሞን ባረጋ ርቀቱን በቀዳሚነት ሲያጠናቅቅ÷ሙክታር እድሪስ ደግሞ 3ኛ ደረጃን ይዞ አጠናቋል፡፡
በምድቡ አዲሱ ይሁኔ 5ኛ ሆኖ ውድድሩን የጨረሰ መሆኑንም ከአትሌቲክስ ፌደሬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡