Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በቤልጂየም የሴቶች 5 ሺህ ሜትር ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸነፉ

አዲስ አበባ፣ ሰኔ 23፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ትላንት ምሽት በቤልጂየም በተካሄደው የሴቶች 5 ሺህ ሜትር ሩጫ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች አሸንፈዋል፡፡

ኢትዮጵያዊቷ መዲና ኢሳ ርቀቱን በ15 ደቂቃ14 ሰከንድ በ01 ማይክሮ ሰከንድ በመጨረስ በቀዳሚነት አጠናቃለች፡፡

ሌላኛዋ አትሌት አሳየች አይቸው ደግሞ ርቀቱን በ15 ደቂቃ በ14 ሰከንድ በ77ማይክሮ ሰከንድ በመጨረስ ሁለተኛ ደረጃ ይዛ ማጠናቀቋን ከአትሌቲክስ ፌደረሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

Exit mobile version