Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ኔቶ ፊንላንድን እና ስዊድንን በአባልነት ለመቀበል ወሰነ

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 23 ፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) የሰሜን አትላንቲክ ጦር ቃል ኪዳን ድርጅት (ኔቶ) ፊንላንድን እና ስዊድንን በአባልነት ለመቀበል ወሰነ።

ጉባኤውን በማድሪድ እያካሄደ ያለው ኔቶ ሁለቱ ሀገራት የአባልነት ስምምነቶችን እንዲፈርሙ ጥሪ አቅርቧል።

ፊንላንድ እና ስዊድን ቃል ኪዳኑን ለመቀላቀል ጥያቄ ማቅረባቸው ይታወሳል።

ይህን ተከትሎ ቱርክ የሀገራቱን የመቀላቀል ፍላጎት ስትቃወም ብትቆይም አሁን ላይ ጥያቄዋን አንስታለች።

ሩሲያ በበኩሏ ሀገራቱ ኔቶን በመቀላቀላቸው የሚያጋጥማት ችግር እንደሌለ መግለጿን አር ቲ ዘግቧል።

ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

 

 

 

Exit mobile version