Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በሎስ አንጀለስ ማራቶን አትሌት ባየልኝ አሸናፊ ሆነ

First place winners for the mens is Bayeligo Teshager from Ethiopia(L) and for the women's is Margaret Muriuki from Kenia, during the 35th LA Marathon at Satan Monica Pier. Sunday March 8,2020. (Photo by Gene Blevins/Contributing photographer)

አዲስ አበባ፣ የካቲት 30፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) ትናንት በሎስ አንጀለስ በተደረገ የማራቶን ውድድር ኢትዮጵያዊው አትሌት ባየልኝ ተሻገር አሸናፊ ሆኗል።
አትሌት ባየልኝ ርቀቱን 2 ሰዓት ከ8 ደቂቃ ከ26 ሰከንድ በመግባት አሸናፊ ሆኗል።
ኬንያውያኑ ጆን ላጋት እና ዊልሰን ቼቤት ደግሞ ሁለተኛ እና ሶስተኛ በመሆን ውድድራቸውን አጠናቀዋል።
የርቀቱ አሸናፊ አትሌት ባየልኝ 53 ሺህ ዶላር ሽልማት ተበርክቶለታል።
በሴቶች በተደረገ ውድድር ደግሞ አትሌት አልማዝ ነገደ 2 ሰዓት ከ32 ደቂቃ ከ28 ሰከንድ በመግባት ውድድሩን ሁለተኛ በመሆን አጠናቃለች።
በተያያዘ ዜና ትናንት በሆላንድ በተደረገ የግማሽ ማራቶን ውድድር ኢትዮጵያዊው አትሌት ዳዊት ወልዴ 1 ሰዓት ከ59 ደቂቃ ከ58 ሰከንድ በመግባት ርቀቱን በበላይነት አጠናቋል።

ምንጭ፦ bleacherreport.com/

Exit mobile version