አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 7፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) ዮርዳኖስ ዓባይ የድሬዳዋ ከተማ አሰልጣኝ ሆኖ መሾሙን ክለቡ አስታወቀ፡፡
ድሬዳዋ ከተማ ከአሰልጣኝ ሳምሶን አየለ ጋር በስምምነት መለያየታቸውን ተከትሎ÷ አሰልጣኝ ዮርዳኖስ ዓባይ ለአንድ ዓመት ክለቡን እንዲያሰለጥን ተሹሟል፡፡
ዮርዳኖስ ጫማውን ከሰቀለ በኋላ ወደ አሰልጣኝነቱ በመግባት በናሽናል ሲሚንት እና ድሬ ዳዋ ፖሊስ የአሰልጣኝነት ሕይወትን የጀመረ ሲሆን÷ ያለፉትን ሁለት ዓመታት በመከላከያ በምክትል አሰልጣኝነት ሲሠራ መቆየቱን ሶከር ዘግቧል፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!