Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ሴኔጋላዊው ሳዲዮ ማኔ የካፍ የዓመቱ ምርጥ አፍሪካዊ እግር ኳስ ተጫዋች ሆኖ ተመረጠ

አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 15፣ 2014 (ኤፍ ቢሲ) የቀድሞው የሊቨርፑል ኮከብ እና የአሁኑ የባየር ሙኒክ አዲስ ፈራሚ ሳዲዮ ማኔ የካፍ የዓመቱ ምርጥ አፍሪካዊ ተጫዋች ሆኖ ተመርጧል፡፡
ሳዲዮ ማኔ በክለቡ ሊቨርፑል ማራኪ የውድድር ዓመት ከማሳለፉ በተጨማሪ÷ ሀገሩ ሴኔጋል የአፍሪካ ዋንጫ ሻምፒዮን እንድትሆን ከፍተኛ አስተዋፅኦ በማድረጉ ነው የካፍ የ2022 ምርጥ ተጫዋች በመሆን የተመረጠው፡፡
በሞሮኮ ራባት በተካሄደው ምርጫ÷ ከሳዲዮ ማኔ በተጨማሪ የሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ አሊዮ ሲሴ የዓመቱ ምርጥ አሰልጣኝ ሽልማትን አሸንፏል፡፡
የሴኔጋል ብሔራዊ ቡድን የዓመቱ ምርጥ ብሔራዊ ቡድን ሽልማትን፣ ዋይዳድ ካዛብላንካ የዓመቱ ምርጥ አፍሪካዊ እግር ኳስ ቡድን ሽልማትን እንዲሁም ማሜሎዲ ሰንዳውንስ የዓመቱ ምርጥ የሴቶች እግር ኳስ ክለብ ሽልማትን አሸንፈዋል፡፡
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version