Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ኬንያውያን ቀጣይ ፕሬዚዳንታቸውን እየመረጡ ነው

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 3፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በኬንያ ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ዛሬ በመካሄድ ላይ ይግኛል።

ተሰናባቹን ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታን ለመተካት እየተካሄደ ባለው ምርጫ አራት እጩዎች ቀርበዋል።

ሆኖም በምርጫው፥ የአሁኑ የሀገሪቱ ምክትል ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ እና የሀገሪቱ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ ዋነኛ ተፎካካሪዎች ናቸው።

ለምርጫው 22 ሚሊየን ኬንያውያን የተመዘገቡ ሲሆን፥ 40 ሺህ የምርጫ ጣቢያዎችም ተቋቁመዋል።

ከፕሬዚዳንታዊ ምርጫው በተጨማሪም ዜጎች የፓርላማ አባላትን እና ሴናተሮችንም በመምረጥ ላይ ይገኛሉ።

 

ምንጭ፦ ቢቢሲ

Exit mobile version