Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

1 ሺህ 20 ኢትዮጵያውያን ከሳዑዲ ዓረቢያ ወደ ሀገራቸው ተመለሱ

አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 4፣ 2014 (ኤፍ ቢ ሲ) በሳዑዲ ዓረቢያ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 1 ሺህ 20 ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው ተመልሰዋል፡፡
ዛሬ በሦስት ዙር በተከናወነ ዜጎችን ከሳዑዲ ዓረቢያ የመመለስ ሥራ ወደ ሀገራቸው ከተመለሱ ዜጎች መካከል ሦስቱ ዕድሜያቸው ከአስራ ስምንት ዓመት በታች የሆኑ ታዳጊዎች መሆናቸውንየውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ አመላክቷል፡፡
ለተመላሽ ዜጎችም ተገቢው ድጋፍ እና እንክብካቤ ተደርጎላቸው ወደ ተዘጋጀላቸው የማቆያ ማዕከላት መሄዳቸው ተመላክቷል፡፡
እስካሁን ድረስ በተከናወነው ዜጎችን ወደ ሀገር የመመለስ ሥራ÷ 63 ሺህ 467 ኢትዮጵያውያንን መመለስ ተችሏል፡፡
ወቅታዊ፣ ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version