Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አቶ ታገሰ ጫፎና የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ም/ፕሬዚዳንት ለስራ ጉብኝት አርባምንጭ ከተማ ገቡ

አዲስ አበባ፣ መስከረም 23፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋና አፈ – ጉባኤ አቶ ታገሰ ጫፎ እና የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ሰለሞን አረዳ ለስራ ጉብኝት አርባምንጭ ከተማ ገብተዋል፡፡

አመራሮቹ አርባምንጭ ከተማ ሲገቡ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት የሥራ ኃላፊዎች እና የጋሞ ዞን ከፍተኛ የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች አቀባበል አድርገውላቸዋል ።

እንግዶቹ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኞች ስልጠና ላይ ይገኛሉ፤ የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አርባምንጭ ማዕከል ይጎበኛሉ እንዲሁም የማዕከሉ የቁልፍ ርክክብ ያካሂዳሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ከጋሞ ዞን መንግስት ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version