Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የኢትዮጵያ አረንጓዴ ልማት ዲፕሎማሲ የወጣቶች ልዑክ ካርቱም ገባ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፍሪካ ወንድማማችነትን እና የአረንጓዴ ልማት ዲፕሎማሲን ዓላማ ለማስተዋወቅ የኢትዮጵያ የወጣቶች ልዑክ ካርቱም ገባ፡፡

ወደ ካርቱም ያመራው የኢትዮጵያ ወጣቶች ልኡካን ቡድን በዴሞክራሲ ሥርአት ግንባታ ማዕከል ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ሙሳ አህመድ ተመርቷል፡፡

ልኡካን ቡድኑ በሚኖረው የሱዳን ቆይታ የአረንጓዴ ልማትንና አፍሪካዊ ወንድማማችነትን የማጠናከር ተልዕኮውን ይወጣልም መባሉን በሱዳን የኢትዮጵያ ኤምባሲ መረጃ ያመላክታል፡፡

በቀጣይ ከሱዳን ወጣቶች ጋር በጋራ የችግኝ መትከል መርሐ-ግብር እና የሁለቱን ሀገራት ትስስር የሚያጠናክር ውይይት እንዲሁም ልምድ ልዉዉጥ ያካሂዳል ተብሏል።

በሱዳን የኢትዮጵያ አምባሳደር ይበልጣል አዕምሮ እና የሱዳን መንግስት ባለሥልጣናት በካርቱም ዓለም አቀፍ አየር መንገድ በመገኘት ልኡካን ቡድኑን ተቀብለዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version