Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ የተመራ የክልሉ ከፍተኛ አመራር የግብርና ልማት ሥራዎችን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 17፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ የተመራ የክልሉ ከፍተኛ አመራር አይሳኢታ አፋንቦ ወረዳዎች የተከናወኑ ያሉትን የግብርና ልማት ሥራዎችን ጎብኝተዋል።

በጉብኝቱም የተለያዩ የግብርና ልማት ስራዎችን፣ የወጣቶችና የሴቶች ማህበር የግብርና ስራ ልማትንም ነው የጎበኙት፡፡

በዚህ ወቅት ወጣቶችን በማበረታታት አስፈላጊውን ድጋፍ እንደሚደረግላቸው ርዕሰ መስተዳድሩ ተናግረዋል ።

ጉብኝቱ በቀጣይ በተለያዩ አካባቢዎች እንደሚቀጥል የአፋር ብዙኃን መገናኛ ዘገባ ያመላክታል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version