Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በደቡብ ክልል በሰሜን ዕዝ ላይ የተፈጸመው ጥቃት ታሰበ

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በደቡብ ክልል ጥቅምት 24 ቀን 2013 ዓ.ም በመከላከያ ሠራዊት የሰሜን ዕዝ ላይ የተፈጸመው ጥቃት መታሰቢያ “መቼም አንረሳውም” በሚል መሪ ቃል ታስቧል፡፡

መታሰቢያው የተዘከረው በደም ልገሳ፣ ገንዘብ በማሰባሰብ እና የሠራዊቱን ጽናት በሚያሳዩ ዝግጅቶች ነው።

በርዕሰ መስተዳድር ጽሕፈት ቤት ግቢ ጧፍ የማብራት ሥነ ስርዓትም ተከናውኗል፡፡

የክልሉ ሕዝብ ለጀግናው መከላከያ ሠራዊት የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል በመታሰቢያው ላይ ተገልጿል፡፡

በመቅደስ አስፋው

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version