Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አሜሪካ በኮሮና ቫይረስ አደጋ ላይ የወደቀውን ኢኮኖሚዋን ለመደገፍ 2 ትሪሊየን ዶላር በጀት አፀደቀች

President Trump speaks while Dr. Anthony Fauci listens during Tuesday's briefing on the coronavirus pandemic at the White House.

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 16፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአሜሪካ ምክር ቤት በኮሮና ቫይረስ ምክንያት አደጋ ላይ የቀደቀውን ኢኮኖሚ ለመደገፍ 2 ትሪሊየን ዶላር በጀት አፀደቀ።

የፀደቀው በጀት የእርዳታ ድርጅቶችን፣ የንግድ ተቋማትን እና የጤና ስርዓቱን ለመደገፍ ይውላል ተብሏል።

ይህንን ፓኬጅ ለማፅደቅ  ከምክር ቤቱ አባላት ጋር ከፍተኛ ድርድር ሲደረግ መቆየቱ ነው የተነገረው።

በአሜሪካ 55 ሺህ ሰዎች በቫይረሱ የተያዙ ሲሆን 800 ሰዎች ደግሞ ህይወታቸው ማለፉ ተጠቁሟል።

ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!
https://t.me/fanatelevision

Exit mobile version