Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

“ከኢትዮጵያ ጎን እቆማለሁ” በሚል የተዘጋጀ ሰላማዊ ሰልፍ በለንደን እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 27፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) “ከኢትዮጵያ ጎን እቆማለሁ” በሚል መሪ ሃሳብ የተዘጋጀ ሰላማዊ ሰልፍ በብሪታኒያ፤ ለንደን በሚገኘው የአሜሪካ ኤምባሲ ለፊት እየተካሄደ ነው።

ሰልፈኞቹ “የሰላም ስምምነቱን እንደግፋለን”፣ “አሜሪካ የሰላም ስምምነቱን መደገፏ በበጎ መልኩ እንቀበለዋለን”፣ “ለአፍሪካ ችግሮች አፍሪካዊ መፍትሔ” የሚሉ መልዕክቶችን እያስተላለፉ ነው።

ሰልፉን ‘ዲፌንድ ኢትዮጵያ ታስክፎርስ ኢሮፕ’ እና በብሪታኒያ የሚገኙ አስተባባሪ ኮሚቴዎች በጋራ እንዳዘጋጁት ኢዜአ ዘግቧል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version