Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የሰላም ስምምነቱን ተከትሎ አገልግሎት መጀመሩ እፎይታ ሰጥቶናል- የጥሙጋ እና አላማጣ ነዋሪዎች

አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 30፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሰላም ስምምነቱን ተከትሎ አገልግሎት መጀመሩ እፎይታ ሰጥቶናል ሲሉ የጥሙጋ እና አላማጣ ነዋሪዎች ተናገሩ።

ፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ያነጋገራቸው ነዋሪዎቹ÷ በጥሙጋ የኤሌክትሪክ እና የሞባይል ኔትዎርክ አገልግሎት መጀመሩን ተናግረዋል፡፡

በኢፌዲሪ መንግሥት እና በህወሓት መካከል የሰላም ስምምነት መካሄዱ እና ስምምነቱን ተከትሎም አገልግሎት በመጀመሩ መደሰታቸውን ገልጸዋል፡፡

ከኤሌክትርክ እና የሞባይል ኔትወርክ በተጨማሪ ሌሎች አገልግሎቶችም እንዲጀመሩ እና የሰብዓዊ ድጋፉንም በፍጥነት የማዳረስ ሥራው ተጠናክሮ እንዲቀጥል ጠይቀዋል።

በሐይማኖት ወንድራድ

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version