Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በጭሮ ወረዳ በተከሰተ የትራፊክ አደጋ የ8 ሰዎች ሕይወት አለፈ

አዲስ አበባ ፣ ሕዳር 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በምዕራብ ሐረርጌ ዞን ጭሮ ወረዳ በተከሰተ የትራፊክ አደጋ የስምንት ሰዎች ሕይወት ማለፉን የዞኑ ፖሊስ መምሪያ አስታውቋል፡፡

አደጋው የተከሰተው ከሐረር ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ የነበረ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ከመኤሶ ሁሴን ወደ ጭሮ በመጓዝ ላይ ከነበረ ባለሦስት እግር ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ ነው፡፡

በመምሪያው የትራፊክ ደኅንነት እና ቁጥጥር ዲቪዥን ኃላፊ ረዳት ኢንስፔክተር ታምራት እሸቱ እንደገለጹት÷ የአደጋው መንስኤ ከፍጥነት በላይ ማሽከርከር ነው፡፡

በተከሰተው አደጋ ሕይወታቸው ካለፉት ስምንት ሰዎች በተጨማሪ በንብረት ላይ ጉዳት መድረሱን ለኦቢኤን ተናግረዋል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡

ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!

Exit mobile version