Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ለሁሉም ሕጻናት ምቹ ኢትዮጵያን ለመፍጠር መሥራት ይገባል – ዶ/ር ኤርጎጌ ተስፋዬ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 11፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ለነገ ሀገር ተረካቢ ሕጻናት ልዩ ድጋፍና እንክብካቤ በማድረግ ለሁሉም ሕጻናት ምቹ የሆነች ኢትዮጵያን ለመፍጠር በትኩረት መሥራት ይገባል ሲሉ ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ ተናገሩ፡፡

የዓለም የሕጻናት ቀን በዓለም ለ33ኛ በኢትዮጵያ ለ17ኛ ጊዜ÷ “ምቹና ሰላማዊት ኢትዮጵያ ለሁሉም ሕጻናት” በሚል መሪ ሐሳብ በሚዛን አማን ከተማ ተከብሯል፡፡

የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ኤርጎጌ ተስፋዬ በአከባበሩ ላይ ባደረጉት ንግግር÷ ለሁሉም ሕጻናት ምቹ የሆነች ኢትዮጵያን ለመፍጠር በትኩረት መሥራት ይገባል ብለዋል፡፡

የሕጻናትን መብት ማክበርና በሥነምግባር አንጾ ማሳደግ እንደሚገባ ገልጸዋል፡፡

በአብዱ ሙሐመድ

Exit mobile version