Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የዓለም ምግብ ፕሮግራም ምግብን ጨምሮ የሕክምና መሳሪያዎች ትግራይ ክልል ማድረሱን አስታወቀ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 16፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የዓለም የምግብ ፕሮግራም ከፈረንጆቹ ሕዳር 15 ጀምሮ 2 ሺህ 400 ሜትሪክ ቶን ምግብ እና 100 ሺህ ሊትር ነዳጅ ትግራይ ማድረሱን ገለጸ፡፡

250 ቶን የሕክምና መሣሪያዎችን በሎጅስቲክሱ በኩል ወደ ክልሉ ማጓጓዙንም ነው ጨምሮ የጠቆመው፡፡

በዓለም የምግብ ፕሮግራም መሪነት የተመድ የዓየር የሰብዓዊ ድጋፍ አቅርቦት አገልግሎቱም ከዛሬ ጀምሮ ወደ መቐለ በረራ መጀመሩንም ነው በገጹ ባሰፈረው መረጃ ያስታወቀው፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version