Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ፈረንሳይ ጥሎ ማለፉን የተቀላቀለች የመጀመሪያዋ ሀገር ሆናለች

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 17፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በ22ኛው የኳታር የዓለም ዋንጫ ምሽት ላይ ፈረንሳይ እና ዴንማርክ የምድብ ሁለተኛ ጨዋታቸውን አድርገዋል፡፡

በዚህም ፈረንሳይ ዴንማርክን 2 ለ 1 በሆነ ውጤት በማሸነፍ ነጥቧን ወደ ስድስት ከፍ አድርጋለች፡፡

የፈረንሳይን የማሸነፊያ ጎሎች ክሊያን ምባፔ በ61ኛው እና 86ኛው ደቂቃ ላይ ማስቆጠር ችሏል፡፡

ዴንማርክን ከሽንፈትያላዳነችውን ብቸኛ ጎል ደግሞ አንድሪያስ ክርስቴንሰን በ68ኛውደቂቃ ላይ አስቆጥሯል፡፡

Exit mobile version