Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ከንቲባ አዳነች በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የ90 ቀናት እቅድ ተግባራት አፈፃፀም ያለበትን ደረጃ ጎበኙ

 

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 18፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ እየተከናወኑ ያሉ የ90 ቀናት እቅድ ተግባራት አፈፃፀም ያለበትን ደረጃ ጎብኝተዋል፡፡

ከንቲባዋ በጉብኝታቸው÷ በክፍለ ከተማው በ90ቀናት እቅድ ተካተው ወደ ተግባር ተገብቶ እየተከናወኑ የሚገኙ የአገልግሎት ማሻሻያና የመልካም አስተዳደር ፕሮጀክቶችን ተመልክተዋል፡፡

እንዲሁም የከተማ ግብርና፣የዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ ላይ የሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎችን ታሣቢ ያደረጉ የጋራ መኖሪያ ቤቶች እንዲሁም ሌሎች ሰው ተኮር ተግባራት በክፍለ ከተማው እየተሠሩ የሚገኙ ፕሮጀክቶችን ጎብኝተዋል።

በጉብኝታቸውም በዘጠና ቀናት እየተሠሩ ያሉ ስራዎች በእቅዳቸው መሠረት እየተከናወኑ እንደሚገኙ መገንዘብ መቻሉን ከከንቲባ ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

 

Exit mobile version