Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በሶማሌ ክልል የሙስና መከላከል ኮሚቴ ተቋቋመ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 24፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሐመድ አምስት አባላት ያሉት የሙስና መከላከል ኮሚቴ አቋቋሙ፡፡

የኮሚቴው ኃላፊነት  በክልሉ በሙስና ተግባራት ላይ ክትትልና ምርመራ  ማድረግ መሆኑ ተገልጿል፡፡

በተደረገው ክትትልና ምርመራ መሰረትም ተሳታፊ ሆነው በተገኙ አካላት ላይ ሕጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ  ኮሚቴው ይሠራል ሲል የክልሉ መገናኛ ብዙኃን ዘግቧል፡፡

 

 

 

Exit mobile version