Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የኦሮሚያ ክልል ሰባት አባላት ያሉት የጸረ ሙስና ኮሚቴ አቋቋመ

አዲስ አበባ፣ ሕዳር 28፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኦሮሚያ ክልል ሰባት አባላት ያሉት የጸረ ሙስና ኮሚቴ አቋቋመ፡፡

 በኦሮሚያ ክልል ሌብነትን እና ብልሹ አሠራርን ለመታገል የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር  ሺመልስ አብዲሳ ሰባት አባላት ያሉት የፀረ ሙስና ኮሚቴ  አቋቁመዋል።

በዚህም መሠረት÷ ኮሚሽነር ጀነራል ከፍያለው ተፈራ ሰብሳቢ እንዲሁም አቶ ጉዮ ዋሪዮ፣ አቶ ተፈሪ ወንዲፍራው፣ ወ/ሮ ኮኮቤ ዲዳ፣ አቶ አብደላ ኦጋቴ፣ ወ/ሮ መሠረት አሰፋ እና ምክትል ኮሚሽነር ዘሪሁን ዱጉማ ደግሞ የፀረ ሙስና ኮሚቴ አባል ሆነው እንዲሠሩ ተሰይመዋል፡፡

የኮሚቴው ሥራ የተሳካ እንዲሆን ህብረተሰቡ አስፈላጊውን ትብብር እና ድጋፍ እንዲያደርግ ርዕሰ መስተዳድር ሺመልስ አብዲሳ ጥሪ አቅርበዋል፡፡

 

Exit mobile version