Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በ3ሺህ ካሬ ሜትር ላይ የሚያርፈው የቂርቆስ ፓርክ ግንባታ ተጀመረ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በ17 ሚሊየን ብር የሚገነባውና በ3ሺህ ካሬ ሜትር ወለል ላይ ያርፋል የተባለው የቂርቆስ ፓርክ ግንባታ ዛሬ በይፋ ተጀምሯል፡፡

ግንባታውን የባንኩ የቦርድ ሰብሳቢ ዶክተር ቢቂላ ሁሩሳ እና ሌሎች የስራ ኃላፊዎች በይፋ አስጀምረውታል፡፡

ቦታው በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 04 ከቄራዎች ድርጅት ፊት ለፊት ያለው ሰፊ ቦታ ሲሆን ፥ ግንባታው በደቡብ ግሎባል ባንክ የሚከናወን መሆኑን ከከተማው ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡

ፓርኩ ግንባታው ሲጠናቀቅ ከመዝናኛነቱ ባሻገር ፣ የንባብ ቦታዎች ፣ የህፃናት መጫዎቻዎች፣ የሻይ ቡናና ቶሎ የሚደርሱ ፈጣን የምግብ አገልግሎቶች፣ የህዝብ መፀዳጃና ሌሎች ስራ ዕድሎችን እንደሚፈጥርም ተገልጿል፡፡

Exit mobile version