Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በኦሮሚያ ክልል ከ810 ሺህ ሄክታር በላይ በመስኖ ስንዴ ተሸፍኗል – አቶ ሽመልስ አብዲሳ

አዲስ አበባ ፣ ታኅሣሥ 14 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል ከ810 ሺህ ሄክታር በላይ በመስኖ ስንዴ መሸፈኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ አስታወቁ።

ርዕሰ መስተዳድሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሁፍ “የግብርና ትራንስፎርሜሽን የወደፊቱ መንገዳችን ነው” ሲሉ ገልጸዋል።

“አርሶ አደሮቻችን እውነተኛ ኢትዮጵያዊ መሆናቸውን በተግባር አሳይተዋል” ብለዋል በጽሁፋቸው።

ርዕሰ መስተዳድሩ የወደፊቱን በተግባር እየገነባን ነው ሲሉም መልዕክታቸውን አስፍረዋል።

Exit mobile version