Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በሀገራዊ የኮሌራ ማስወገድ እቅድ ትግበራ ላይ አውደ ጥናት እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 17፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በሀገራዊ የኮሌራ በሽታ ማስወገድ እቅድ ትግበራ ላይ አውደ ጥናት እየተካሄደ ነው፡፡
 
እቅዱ የጤና ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ የሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ከውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር፣ ከዓለም ጤና ድርጅት እና ከዩኒሴፍ ጋር በመተባበር ያዘጋጁት መሆኑ ተመላክቷል፡፡
 
በመድረኩ የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰን ጨምሮ ሌሎች የመንግስት የሥራ ሃላፊዎች እና የአጋር አካላት ተወካዮች ተገኝተዋል፡፡
 
በአውደ ጥናቱ የኮሌራ በሽታን ለመቆጣጠር ሁሉን አቀፍ እና ዘርፈ ብዙ የመከላከል ዘዴን መከተል እንደሚገባ ተገልጿል፡፡
 
 
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version