Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በአዳማ ከተማ በደረሰ ፍንዳታ የአንድ ሰው ህይወት አለፈ

አዲስ አበባ፣ ታኅሣሥ 18፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዳማ ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማ ደደቻ አራራ ቀበሌ ጉዲሳ በተባለው ሆቴል በተከሰተዉ ፍንዳታ የአንድ ሰው ህይወት ማለፉን የኦሮሚያ ኮሙኒኬሽን አስታወቀ፡፡

በአደጋው በሶስት ሰዎች ላይ የመቁሰል አደጋ መድረሱም ተመላክቷል፡፡

ፈንዳታውን አድርሰዋል የተባሉ ተጠርጣሪዎች በፖሊስ ቁጥጥር ስር ውለው ምርመራ እየተካሄደባቸው መሆኑ የተገለፀ ሲሆን÷ በሆቴሉ አካበቢ ያለው ማህበረሰብ ለመርማሪ ፖሊሶች አስፈላጊውን መረጃ በመስጠት ትብብር እንዲያደርግ ጥሪ ቀርቧል፡፡

Exit mobile version