Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

አምባሳደር ምሥጋኑ አረጋ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው ተሾሙ

አዲስ አበባ፣ ጥር 3፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ አምባሳደር ምሥጋኑ አረጋን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አድርገው ሾሙ፡፡

አምባሳደር ምሥጋኑ አረጋ ከጥር 02 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው መሾማቸውን ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

አምባሳደር ምሥጋኑ አረጋ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው እስከ ተሾሙበት ጊዜ ድረስ የኢትዮ-ኢንጂነሪንግ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ሲያገለግሉ መቆየታቸው ተመላክቷል።

አምባሳደር ምሥጋኑ ከአሁን በፊት በኳታር እና በተባበሩት ዓረብ ኤምሬቶች የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ሆነው ማገልገላቸውን የሚታወስ ነው፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version