Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ፕሬዚዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ የ7 ሀገራት አምባሳደሮችን የሹመት ደብዳቤ ተቀበሉ

አዲስ አበባ፣ ጥር 5፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢፌዴሪ ፕሬዚዳንት ሣህለ ወርቅ ዘውዴ የሰባት ሀገራት አምባሳደሮችን የሹመት ደብዳቤ ተቀበሉ፡፡

የሹመት ደብዳቤያቸውን ለፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ዘውዴ ያስረከቡት የሮማንያ አልጄሪያ ቼክ ሪፐብሊክ ጊኒ ዚምባብዌ ጊኒ ቢሳኦ እና እንግሊዝ አምባሳደሮች ናቸው፡፡

አምባሳደሮቹ ከፕሬዚዳንት ሣህለወርቅ ጋር በነበራቸው ቆይታ የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን በሚያጠናክሩበት መንገድ ላይ መምከራቸውን ኢቢሲ ዘግቧል፡

Exit mobile version