Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በመዲናዋ የጥምቀት በዓል ተከብሮ እስኪጠናቀቅ ሞተር ብስክሌት ማሽከርከር ተከለከለ

አዲስ አበባ፣ ጥር 8፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ የጥምቀት በዓል ምክንያት በማድረግ ከዛሬ ጥር 8 ቀን 6 ሠዓት ጀምሮ እስከ ሐሙስ ጥር 11 ቀን 2015 ዓ.ም አመሻሽ 12 ሠዓት ድረስ ሞተር ብስክሌትን ማሽከርከር ፍጹም የተከለከለ መሆኑን የትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ አስታውቋል፡፡

ክልከላው የሚመለከተው የፀጥታ እና የትራፊክ ቁጥጥር ሥራ አካላት ከሚጠቀሙባቸው ሞተር ብስክሌቶች ውጪ በአዲስ አበባ ከተማ በሁሉም አካባቢዎች የሚንቀሳቀሱትን ባለሁለት እግር ሞተር ብስክሌቶች በሙሉ ነው፡፡

የሞተር ብስክሌት ባለንብረቶችም ሆኑ አሽከርካሪዎች ይሄንኑ ክልከላ መሰረት በማድረግ እስከ ተጠቀሰው ቀን ድረስ በትዕግስት እንዲጠብቁ ኤጀንሲው አሳስቧል፡፡

ይህንን መልዕክት በሚተላለፉ አካላት ላይም ጥብቅ እርምጃ እንደሚወስድ ነው ኤጄንሲው ያስታወቀው፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version