አዲስ አበባ፣ ጥር 16፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 2015 ከተቋረጠበት የሚጀመርበት ቀን ለአንድ ሣምንት ተራዘመ፡፡
በአዳማ ከተማ የሚካሄደው ቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ጥር 20 ቀን 2015 ዓ.ም እንደሚጀመር የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማኅበር መግለጹ ይታወሳል፡፡
ይሁን እንጅ ውድድሩ የሚጀመርበት ቀን ቀድሞ ከተገለፀው በአንድ ሣምንት መራዘሙን ከማኅበሩ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡