Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በአቶ አህመድ ሺዴ የተመራ ልዑክ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ቻይና ገባ

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 14 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አህመድ ሺዴ የተመራ ልዑክ ለይፋዊ የሥራ ጉብኝት ቻይና ቤጂንግ ገብቷል።

ልዑኩ በቆይታው በሀገራቱ የንግድ፣ ኢንቨስትመንት እና ኢኮኖሚ ትብብር ጉዳዮች ላይ ይመክራል ተብሎ ይጠበቃል።

ከዚህ ባለፈም ከሀገሪቱ የገንዘብ ተቋማት እና የኢንቨስትመንት ኩባንያዎች ጋር ስትራቴጂካጂካዊ ውይይት እንደሚያደርጉ በቻይና የኢትዮጵያ ኤምባሲ አስታወቋል።

በተጨማሪም ልዑኩ በሀገራቱ የጋራ ኢኮኖሚ እና የንግድ ኮሚሽን እንዲሁም የኢትዮጵያ ኤምባሲ ባዘጋጀው የኢትዮ ቻይና የኢንቨስትመንት ፎረም ላይ እንደሚሳተፍም ነው የሚጠበቀው።

ልዑኩ አቶ አህመድ ሺዴን ጨምሮ፥ የብሄራዊ ባንክ ገዥ ማሞ ምህረቱ፣ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን ሌሊሴ ነሜ፣ የገንዘብ ሚኒስትር ዴኤታ ኢዮብ ተካልኝን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎችን ያካተተ ነው።

Exit mobile version