Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የአውሮፓ ኮሚሽን ሠራተኞች ቲክቶክ እንዳይጠቀሙ ታገዱ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 17፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)የአውሮፓ ኮሚሽን ሠራተኞቹን ቲክቶክ እንዳይጠቀሙ አገደ፡፡

መተግበሪያውን ከሞባይላቸውም ሆነ ከኮሚሽኑ መገልገያ ኮምፒውተሮች ላይ እንዲያጠፉ መታዘዛቸውን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡

ኮሚሽኑ ውሳኔውን ያሳለፈው የድርጅቱን የሳይበር ደኅንነት ለማሳደግ እና ዲጂታል ሠነዶቹን ከጥቃት ለመታደግ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡

ኮሚሽኑ ከ32 ሺህ በላይ ቋሚና ጊዜያዊ ሠራተኞች እንዳሉት አስታውቋል፡፡

ቲክ ቶክ የተሰኘው የማኅበራዊ መገናኛ የቻይናው ባይትዳንስ ኩባንያ መሆኑ የተጠቆመ ሲሆን የተጠቃሚዎቹን መረጃ ለቻይና መንግስት ያቀርባል የሚል ክስ ይቀርብበታል።

ቲክቶክ በበኩሉ ማኅበራዊ ሚዲያው ከሌሎች ማኅበራዊ ሚዲያዎች የተለየ እንደማይሰራ ገልጿል።

የኮሚሽኑ ሰራተኞች የቲክ ቶክ መተግበሪያ ያለበትን የግል ስልካቸውንም ቢሆን መጠቀም አይችሉም ነው የተባለው።

ከዚህ ጋር ተያይዞም ሰራተኞቹ ቢበዛ እስከ ፈረንጆቹ መጋቢት 15 ድረስ ቲክ ቶክን ከስልኮቻቸው ማስወገድ ይኖርባቸዋል።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version