Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የሩሲያ ኩባንያ ተወካዮች የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 29፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) ኢትዮጵያ ውስጥ በሚገኙ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ገብተው የማምረት ፍላጎት ያላቸው የሩሲያ ኩባንያ ተወካዮች የኢንዱስትሪ ፓርኮችን ጎበኙ፡፡

የሩሲያ ኩባንያ ተወካዮች ከኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን አመራሮች ጋር የቦሌ ለሚ ኢንዱስትሪ ፓርክን አጠቃላይ የስራ እንቅስቃሴ ተመልክተዋል፡፡

እንዲሁም ለፋርማሲዩቲካል ሴክተር የተገነባውን የቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርክ አጠቃላይ የስራ እንቅስቃሴ እና ምቹ ሁኔታዎችን እንደሚመለከቱ ከኮርፖሬሽኑ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

Exit mobile version