Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ኢትዮጵያና ኖርዌይ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የሚያከናውኗቸውን ተግባራት ለማጠናከር ተስማሙ

አዲስ አበባ ፣ የካቲት 30 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኖርዌይ ዓለም አቀፍ የአየር ንብረትና የደን ልማት ኢኒሼቲቭ ቡድን አባላት ከፕላንና ልማት ሚኒስቴር ከፍተኛ የስራ ሃላፊዎች ጋር ተወያይተዋል፡፡
 
በውይይታቸውም በሀገራቱ መካከል ያለውን የሁለትዮሽ ግንኙነት ማሳደግ በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ መክረዋል፡፡
 
በተለይም ኖርዌይና ኢትዮጵያ በአየር ንብረት ለውጥ ላይ የሚሰሯቸውን የጋራ ተግባራት እንደሚያጠናክሩ መግለጻቸውን ከሚኒስቴሩ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡
Exit mobile version