Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

ጨረቃ ባለመታየቷ የረመዷን ጾም ሐሙስ ይጀምራል

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 12፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የ1444ኛው ዓመተ ሒጅራ የረመዷን ጾም ጨረቃ ባለመታየቷ ሐሙስ (ከነገ በስቲያ) ይጀምራል፡፡

የረመዷን ጾም ዛሬ (ማክሰኞ) ጨረቃ ባለመታየቷ ነው የፊታችን ሐሙስ(ከነገ በስቲያ) የሚጀምረው፡፡

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት የ1444ኛው ዓመተ ሒጅራ የረመዷን ጾምን አስመልክቶ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፏል።

በመልዕክቱም÷ሙስሊሙ ሕብረተሰብ በጾም ወቅት የተለመደውን የእርስ በርስ የመደጋገፍ እና የመረዳዳት ተግባሩን በጾም ወቅት አጠናክሮ እንዲቀጥልበት ጠይቋል።

 

 

Exit mobile version