Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የኤርትራ የጦር ጀነራሎችና ከፍተኛ መኮንኖች የከንቲባ ፅህፈት ቤትን ጎበኙ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 27፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በጀነራል አብርሃ ካሳ የተመራው የኤርትራ የጦር ጀነራሎችና ከፍተኛ መኮንኖች የልዑካን ቡድን የከንቲባ ፅህፈት ቤትን ጎበኘ፡፡

የአዲስ አበባ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው “የኤርትራ የጦር ጀነራሎች እንኳን ወደ ሁለተኛ ቤታችሁ መጣችሁ ለማለት እወዳለሁ”ብለዋል::

ልዑኩ ከተማ አስተዳደሩ ለተገልጋዩ የተቀላጠፈ አገልግሎት ለመስጠት የሰራውን ስራዎች መጎብኘቱን ገልፀዋል፡፡

Exit mobile version