Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የኤርትራ ልዑክ በማዕድን ዘርፍ የተሰሩ የሪፎርም ሥራዎችን ጎበኘ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 27፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በጀነራል አብርሃ ካሳ የተመራው የኤርትራ የጦር ጀነራሎችና ከፍተኛ መኮንኖች ልዑክ የማዕድን ሚኒስቴር የሠራቸውን የሪፎርም ሥራዎች ጎብኝቷል፡፡

በጉብኝቱ ወቅትም በማዕድን ዘርፍ የተሠሩ የሪፎርም ሥራዎችና የወደፊት ዕቅዶች ለልዑካን ቡድኑ አባላት ገለጻ ተደርጎላቸዋል፡፡

ልዑኩ የኢትዮጵያ ማዕድን ጋለሪን መጎብኘቱን እና ሚኒስቴሩ ያከናወናቸውን የሪፎርም ሥራዎች ማድነቁን የማዕድን ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል፡፡

Exit mobile version