Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማት ዝቅተኛ የተከፈለ ካፒታል መጠን ወደ 75 ሚሊየን አደገ

አዲስ አበባ፣ መጋቢት 27፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ የማይክሮ ፋይናንስ ተቋማትን ዝቅተኛ የተከፈለ ካፒታል መጠን ከ50 ሚሊየን ወደ 75 ሚሊየን አሳደገ።

ባንኩ ከዚህ ውሳኔ የደረሰው ወቅታዊውን ሀገራዊ የማክሮ ኢኮኖሚ ሁኔታ እና የተቋማቱን አቅም አገናዝቦ መሆኑ ተገልጿል፡፡

በኢትዮጵያ የተረጋጋ የኢኮኖሚ ዕድገት መኖሩ እንዲሁም እየጨመረ የመጣው የብድር ፍላጎት ለውሳኔው በምክንያትነት መነሳቱን የባንኩ መረጃ ያመላክታል፡፡

እንዲሁም በዘመናዊው የፋይናንስ የመሠረተ ልማት እና አቅርቦት ዘርፍ መዋዕለነዋይ ለማፍሰስ እያደገ የመጣው ፍላጎት በምክንያትነት ተጠቅሰዋል፡፡

ውሳኔው ከፈረንጆቹ ጥር 16 ቀን 2023 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ መደረጉም ነው የተመለከተው፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version