Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የኦሮሚያ እና ሶማሌ ክልሎችን ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ ውይይት እየተካሄደ ነው

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 6፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የኦሮሚያ እና ሶማሌ ክልሎች ተጎራባች አካባቢዎችን ግንኙነት ለማጠናከር ያለመ ውይይት በድሬዳዋ እየተካሄደ ነው።

ውይይቱን እየመሩ የሚገኙት የአሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሽመልስ አብዲሳ እና የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ ናቸው፡፡

በውይይቱ ላይ የሁለቱም ክልሎች ከፍተኛ አመራሮችና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር መገኘታቸውን ኢዜአ ዘግቧል፡፡

ይህም የሁለቱን ክልሎች ሁለንተናዊ ግንኙነት አጠናክሮ ወደ ላቀ ደረጃ ለማሻገር የሚያግዝ መሆኑ ነው የተመለከተው፡፡

Exit mobile version