Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

በኦሮሚያ ከግንቦት 1 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ሥርዓት ብቻ ይከናወናል

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 14፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በኦሮሚያ ክልል ከግንቦት 1 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ የነዳጅ ግብይት በኤሌክትሮኒክስ ሥርዓት ብቻ እንደሚከናወን የክልሉ ንግድ ቢሮ አስታወቀ፡፡

በኤሌክትሮኒክስ የሚከነወነው የነዳጅ ግዥና ሽያጭ የተሳለጠ እንዲሆንም የሚመለከታቸው አካላት ከወዲሁ ዝግጁ እንዲሆኑ ሲል ቢሮው አሳስቧል፡፡

በሌላ በኩል እንደ አቢሲያ ካርድ ኩፖን እና ሌሎች የግብይት መፈጸሚያ ዘዴዎች ሲጠቀሙ የነበሩ ተቋማት እስከያዝነው በጀት ዓመት መጨረሻ ድረስ ብቻ መጠቀም እንደሚችሉ ነው የተገለጸው፡፡

ኔትወርክ በሌለበት አካባቢም ሲ ቢ ኢ ብር በመጠቀም የነዳጅ ግብይት መፈጸም እንዲቻል ከቴሌ ጋር ስምምነት ላይ ተደርሶ መተግበሪያው መበልጸጉን የኦሮሚያ ክልል ኮሙኒኬሽን ቢሮ መረጃ ያመላክታል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version