Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የሀረሪ ክልል ካቢኔ ከሸዋል ኢድ በዓል ጋር በተያያዘ እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎችን ገመገመ

አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 17፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የሀረሪ ክልል ካቢኔ ከሸዋል ኢድ በዓል ዝግጅቶችና ከበዓሉ ጋር በተያያዘ እየተከናወኑ የሚገኙ ስራዎችን ገምግሟል።

በዚህም በእለቱ የሚመረቁ ፕሮጀክቶችን፣ የክልሉን የቱሪስት መዳረሻ ስፍራዎችን፣ የጽዳትና ውበት ስራዎችንና የአገልግሎት መስጫ ማእከላት ሁኔታን ምልከታ በማድረግ አፈፃፀማቸው ተገምግሞ አቅጣጫ ተቀምጧል ነው የተባለው።

በተደረገው የመስክ ግምገማም የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ኦርዲን በድሪን ጨምሮ የክልሉ የካቢኔ አባላት መገኘታቸውን ከክልሉ ኮሙኒኬሽን ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

በክልሉ ከቀናት በኋላ የሸዋል ኢድ በዓል በድምቀት ይከበራል፡፡

Exit mobile version