አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 30፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) በቤትኪንግ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 23ኛ ሳምንት መርሐ-ግብር ሁለት ጨዋታዎች ተካሂደዋል፡፡
ወላይታ ድቻና አዳማ ከተማ በሃዋሳ ዩኒቨርሲቲ ስታዲየም ባደረጉት ጨዋታ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል፡፡
የአዳማ ከተማን ግብ ዮሴፍ ታረቀኝ 65ኛው ደቂቃ ላይ ሲያስቆጥር÷የወላይታ ድቻን ደግሞ ቢኒያም ፍቅሩ 82ኛው ላይ አስቆጥሯል፡፡
በተመሳሳይ ምሽት12 ሰዓት ላይ ጨዋታቸውን ያደረጉት ፋሲል ከነማ እና አርባ ምንጭ ከተማ 1 ለ 1 በሆነ አቻ ውጤት ተለያይተዋል።
የአርባ ምንጭ ከተማን ግብ ተመስገን ደረሰ ከእረፍት በፊት ሲያስቆጥር÷ የፋሲል ከነማን ደግሞ በዛብህ መለዮ በ78ኛው ደቂቃ ላይ አስቀጥሯል፡፡
ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን