Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የአትላንታ ከንቲባ “ክሪኤቲቭ ሃብ ኢትዮጵያ” የተሰኘውን ማዕከል ጎበኙ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 4 ፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ) የአሜሪካ የአትላንታ ከተማ ከንቲባ አንድሬ ዲከንስ የኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት የ“ክሪኤቲቭ ሃብ ኢትዮጵያ” ማዕከልን ጎበኙ፡፡

በከንቲባው የተመራው የልዑካን ቡድን በማዕከሉ በመገኘት በወጣት ሥራ ፈጣሪዎችና የፈጠራ ባለቤቶች የተሰሩ የፈጠራ ውጤቶችን መጎብኘታቸውንም የኢንተርፕራይዙ መረጃ አመላክቷል፡፡

ከንቲባ አንድሬ ዲከንስ በኢትዮጵያ ለስራ ፈጣሪዎች ምቹ ዕድሎች መኖራቸውን ጠቅሰው፥ የፈጠራ ሐሳቦች ወደ ገንዘብ እንዲለወጡ በትብብር እንደሚሰሩ ገልጸዋል።

“ክሪኤትቭ ሃብ ኢትዮጵያ” አዳዲስ ሐሳብ ያላቸው ወጣት ሥራ ፈጣሪዎች ሐሳባቸውን ወደ ተግባር መለወጥ እንዲችሉ የተለያዩ ድጋፎችን እያደረገ የሚገኝ ማዕከል ነው።

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/fanabroadcasting
ዩትዩብ፦ https://www.youtube.com/c/fanabroadcastingcorporate/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ኢንስታግራም፦ https://www.instagram.com/fana_television/
ቲክቶክ፦ https://www.tiktok.com/@fana_television
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን
Exit mobile version