Site icon Welcome to Fana Broadcasting Corporate S.C

የኢትዮጵያን የግብርና ምርት ወጪ ንግድ በጂቡቲ በኩል ማቀላጠፍ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ተመከረ

አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 13፣ 2015 (ኤፍ ቢ ሲ)የኢትዮጵያን የግብርና ምርት ወጪ ንግድ በጂቡቲ በኩል ማቀላጠፍ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ምክክር ተካሄደ፡፡

በጉዳዩ ላይ የኢፌዴሪ የግብርና ሚኒስትር ዴኤታ ሶፊያ ካሳ (ዶ/ር) እና በጂቡቲ የዶራሌ ወደብ ዋና ሥራ አሥፈፃሚ ጃማ ኢብራሂም ተገናኝተው መክረዋል፡፡

በሁለቱ ወገኖች መካከል የተካሄደው ውይይት ፍሬያማ እንደነበረ ሚኒስትሯ መግለጻቸውን በጂቡቲ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል፡፡

የተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ተነስተው በዋና የትኩረት ነጥቦች ላይ የተሻሻለ አሠራር ለመዘርጋት መስማማታቸውም ተጠቁሟል፡፡

ወቅታዊ፣ትኩስ እና የተሟሉ መረጃዎችን ለማግኘት፡-
ድረ ገጽ፦ https://www.fanabc.com/
ቴሌግራም፦ https://t.me/fanatelevision
ትዊተር፦ https://twitter.com/fanatelevision በመወዳጀት ይከታተሉን፡፡
ዘወትር፦ ከእኛ ጋር ስላሉ እናመሰግናለን!
Exit mobile version